Tuesday, October 31, 2017

Successful Marriage not divorce 2

አንድ በሚስቱ በጣም የተማረረ ባል ሳይኮሎጂስት ጋር ይሄዳል…
ሳይኮሎጂስት ፡- እሺ ጌታው ለመኖር ምንድ ነው የምትሰራው ?
ባል ፡- ባንክ ቤት ውስጥ ማናጀር ነኝ
ሳይኮሎጂስት ፡- እሺ ባለቤትህስ ምንድ ነው ምትሰራው ?
ባል ፡- እሷ ባክህ ምንም አትሰራም የቤት እመቤት ነች
ሳይኮሎጂስት ፡- ጠዋት ለቤተሰቡ ቁርስ ሚሰራው ማነው ?
ባል ፡- ሚስቴ ነቻ ምክንያቱም ምንም ስራ የለባትም..
ሳይኮሎጂስት ፡- ሚስትህ ጠዋት ከእንቅልፏ ስንት ሰአት ነው ምትነሳው ?
ባል ፡- ለሊት 11፡00 ሰአት አካባቢ ነው ምትነሳው ቁርስ ከመስራቷ በፊት ቤት ስለምታጸዳ ቀደም ብላ ነው ምትነሳው…..
ሳይኮሎጂስት ፡- ልጆችህ ትምህርት ቤት ሚሄዱት እንዴት ነው ?
ባል ፡- ሚስቴ ስራ ስለሌላት እሷ ነች የምትወስዳቸው
ሳይኮሎጂስት ፡- ልጆችህን ትምህርት ቤት ከወሰደደች በኋላ ምን ትሰራለች ?
ባል ፡- ከወሰደቻቸው በኋላ ያው ስራ ስለሌለባት ወደ ገበያ ሄዳ ምሳ የሚሰራበትን ነገር ትገዛዛና ምሳ ከሰራች በኋላ ልብስ ታጣጥብና እረፍት ታረጋለች በቃ ምንም ምትሰራው ስራ የላትም
ሳይኮሎጂስት ፡- አንተ ማታ ከስራ ስትመለስ ምን ታረጋለህ ?
ባል ፡- እኔ ስራ ደክሜ ስለምገባ በቃ ሻወር እወስድና ረጋ ብዬ ከልጆቼ ጋር እቀመጣለሁ
ሳይኮሎጂስት ፡- የዛኔ ሚስትህ ምን ትሰራለች ?
ባል ፡- ለቤተሰቡ ራት ታቀርብና እቃ ታጣጥብና ልጆቹን አስተኝታ ወደ እንቅልፍ ትሄዳለች
ሳይኮሎጂስት ፡-እሺ ከአንተና ከሚስትህ ማን በጣም የሚሰራ ይመስልሃል የሚስትህ ውሎ ከንጋቱ 11 ሰአት የጀመረ እስከ ማታ ድረስ የሚቀጥል ነው፡፡ ታዲያ ይሄንን ነው ስራ ስለሌለባት የምትለው !!!! አዎ በርግጥ የቤት እመቤት ለመሆን ትምህርት ቤት ገብቶ ሰርተፍኬት መቀበል ላያስፈልገው ይችላል፡፡ ግን በሕይወታችን ውስጥ የነሱ አስተዋጽኦ በጣም አስፈላጊ ነው፡፡
Appreciate your wife's because their sacrifices is uncountable.
ስለ ሴቶቻችን…..
• ፀጥ ስትል ብዙ ሚሊዮን የሚሆኑ ሃሳቦችን እያሰበች እያብሰለሰለች መሆኑን ይግባህ፡፡
• አፍጣ ስታይህ ለምን እንደዚ እንደምትወድህ እና ይህን ሁሉ መስዋትነትን እንደምትከፍልልህ እያሰበች ነው፡፡
• አብሬህ እቆማለው ስትልህ ማዕበል እንኳን ቢመጣ አልንቀሳቀስም ማለቷ ነው፡፡
• አትጉዳት ወይም በተሳሳተ መንገድ አታስባት….አንተ ስትራብ ተርባ ስትቸገር ተቸግራ ስትራቆት ተራቁታ ገበናህን ሸፍና የምትኖረው ሚስትህ የልጆችህ እናት ሚስትህ ናት፡፡ አረ እውነታውን ልንገርህ ሚስትህ ማለት የቤትህ ብርሀን ናት።
ስለዚህ አክብራት ውደዳት ፍቅርን ስጣት፡
«ሼር በማድረግ ለወዳጆ ያካፍሉ»

Successful Marriage not divorce 1

ውዷ እህቴ *ለባልሽ* 17 ነገሮች!!

1/ ግትርነትን ተጠንቀቂ፣ መልካም ትዳርን ያናጋል።

ባልሽን ወንድነቱን የተፈታተንሽው ይመስለዋል።

2/ ሙግትነትን ተጠንቀቂ፣ ሙግት ትልቅ በሽታ ነው።

3/ ሌሎችን አትመልከች እንደቤትሽ አብቃቅተሽ መኖር ልመጂ።

4/ አቀባበልሽን አሳምሪ፤ ዋናው የፍቅር ማጠንከሪያ ነው። (ከፍትፍቱ ፊቱ)

5/ ለስለስ ያለ ባህሪ ይኑርሽ። ተወዳጅ ያደርግሻልና።
ጥሩ ስራ ስታይበት በደስታ ግለጪለት።

6/ ያየሽውንና የሰማሽውን ሁሉ አታውሪለት ወንድ ብዙ ወሬ አይወድምና።

ሚስጥሩን ጠብቂለት በሁሉም በኩል ሚዛናዊ ሁኚ ዘውድ የተጫናት ንግስት ያደርግሻል።

7/ በሱ በኩል በሰጠሽ ፀጋ አላህን አመስግኚ።

8/ ምንግዜም ውበትሽን ጠብቂ። አንቺ ከባልሽ ብዙ ነገሮችን እንደምትፈልጊ እሱም ካንቺ ይሻል! ብዙ ጊዜ ሴት እቤቷ በምትውልበት ቀን የማድ-ቤት ስራ ይዞሽ ትውይ ይሆናል ባለቤትሽ ወደቤት ሲመጣ ተዘጋጅቶ የሚጠብቀው የሚበላ የሚጠጣ ነገሮች ብቻ ናቸው።

የሚበላና የሚጠጣ እኮ እውጪም አይጠፋ እህቴ ነው ወጭ ለመቀነስ አይደለም ለሱ ከምግቡም ከምኑም ይልቅ ያንቺ ታጥቦና ተኩሎ ለሱ ከምንም በላይ ነው።

9/ ብዙ ግዜ ልብ የማንላቸው ነገሮች አሉ። ፈጅር ላይ ከመኝታ ተነስተን ልብስ ለብሰን የሆነ ነገር ቁርስ ሰርተሽ ባለቤትሽ ለስራ ከወጣ ቡሃላ አንቺም
በቤቱ ስራ ጎንበስ ቀና ስትይ ያንኑ የበለበሽውን ልብስ ሳታወልቂው ማታ ተመልሶ ይመጣል።

ያኡክቲ ይሄ አግባብ አይደለም። የበለጠ ውብ ሆነሽ ቆይው ባለቤትሽ አንቺን ሲያይሽ እንዲደሰት አርጊው።

10/ ወንድ ልጅ በውበት እንደሚማረክ እወቂ። እናም ባለቤትሽ ሌላውብ እንዳያይ አንቺ ውብ ሁኚ እራስሽን ጠብቂ።

11/ ሀዘንም ጭንቀትም ቢሆን ያንቺ እንደዛ መሆን ሁሉን ያቀልለታል። አስታውሽ የሰሃባዋን ኡሙ ሰለይማን ረ.ዓ ታሪክ የልጇን እሬሳ አስተኝታ ለባሏ እንዴት ውብ ሆና እንደጠበቀችው።
አየሽ እህቴ የባል ሀቅ እስከዚህ ድረስ ነው።

12/ ከማግባትሽ በፊት ውብ ትሆኚ አልነበር አሁን ቤትሽን ብቻ ማስዋብ አይሁን ስራሽ አንቺም ውብ ሁኚ። ከበፊቱ ውብ መሆኛሽ አሁን ነው።
13/ ሀላፊነት አለብሽ ለባልሽ ማራኪ የመሆን።

14/ ቤትሽን (ትዳርሽን) የበለጠ የሚያደምቀው በቁሳቁስ አይደለም። አንቺ ባልሽን ስታስደስቺ ነው።

15/ ያጠፋውን ነገር ብቻውን ቀስ ብለሽ ንገሪው።

ሀቁን ጠብቂ ተበሳጭቶ ሲገባ አረጋጊው።
16/ ደስተኛ በሆናችሁበት ሰዓት እንደምቶጂውም ንገሪው።

17/ ምንግዜም በዱአሽ እንዳትረሽው።
ለዲኑም እንዲጠነክር እርጂው።

ያገባችሁ አላህ ጥሩ ሚስት ያድርጋችሁ ያላገባችሁ አላህ ጥሩ ትዳር ይወፍቃችሁ።

Thursday, October 12, 2017

Inter country Adoption in Ethiopia

የውጭ አገር ጉዲፈቻ የተፈጥሮ ቤተሰብ ፍቅርና እንክብካቤን ሙሉ በሙሉ የማይተካና ከዚህ ቀደም በጉዲፈቻ ወደ ውጭ አገራት የሄዱ ህፃናት ላይ የማንነት ቀውስ በማስከተሉ፣ ይህን አሠራር የሚፈቅደው የሕግ ድንጋጌ ከቤተሰብ ሕጉ እንዲሠረዝ መንግሥት ወሰነ።

http://new.ethiopianreporter.com/article/1881

Tuesday, October 21, 2014

the enforcemnt and supervision of offenders released on pardon in Ethiopia


you can read more on  the enforcement  and supervision  of offenders released on pardon in Ethiopia. what are the rights and duties of offenders released on pardon? when is revocation justified? can we say offenders released on pardon are to be dealt with those released on probation? do we need some sort of mechanism to supervise? for more issues you can read and comment just click the link here the enforcement and supervision of offenders released on pardon in Ethiopia

Friday, October 17, 2014

Ethiopian justice. law and research


 for a comprehensive explanation on ethiopian legal and justice system you can read more. just click here------Guide to Ethiopian Law and Justice

Monday, December 2, 2013

የመጀመሪያ ደረጃ መደበኛ የፍትሐብሔር ክርክሮች አካሄድ (General outline for first instance ordinary civil proceedings)

የመጀመሪያ ደረጃ መደበኛ የፍትሐብሔር ክርክሮች አካሄድ (General outline for first instance ordinary civil proceedings)
  1.   የክስ አቤቱታ (ከሰነድና ከፅሁፍ ማስረጃ እንዲሁም ከማስረጃ ዝርዝር ጋር) ይቀርባል፡
  2. ተከሳሹ የመከላከያ መልሱን ይዞ እንዲቀርብ ይታዘዛል፡፡
  3. የመከላከያ መልስ (ከሰነድና ከጽሑፍ ማስረጃ እንዲሁም ከማስረጃ ዝርዝር ጋር) ይቀርባል፡፡ 
  4. የመከላከያ መልሱ ከቀረበ በኋላ የጽሑፍ ክርክሩ ያቆማል፡፡
  5. የጽሑፍ ክርክሩ ከቆመ በኋላ ክሱን ለመስማት ይቀጠራል፡፡
  6. በተቀጠረው ቀን ባለጉዳዮች ራሳቸው ወይም ወኪሎቻቸው ይቀርባሉ፡፡ 
  7. ባለጉዳች ከፅሑፍ አቤቱታቸው ጋር ያላቀረቡትን የፅሁፍ ማስረጃ ይዘው ይቀርባሉ፡፡  
  8. የጽሑፍ ማስረጃ ሁሉ በባለጉዳች ወይም በፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ ተጠቃሎ ይገባል፡፡ፍርድ ቤቱ ባለጉዳዮችን ወይም ወኪሎቻቸውን ይመረምራል፡፡ የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ ከቀረበ ውሳኔ ይሰጥበታል፡፡
  9. በተደረገው ምርመራ ተከሳሹ የቀረበበትን ክስ ካመነ ወዲያውኑ ውሳኔ ይሰጣል፡፡
  10.  ተከሳሹ የቀረበበትን ክስ ካላመነ የክርክሩ ጭብጥ ይያዛል፡፡
  11.  ጭብጡ ከተመሠረተ በኋላ ክርክሩን መስማትና ማስረጃ መመርመር ይቀጥላል፡፡
  12. ለሁለቱም ወገን ምስክሮች መጥሪያ ይላካል፡፡
  13. የሁለቱም ወገን ምስክሮች ተሟልተው ይቀርባሉ፡፡
  14. ከሳሹ (በተወሰኑ ሁኔታዎች ተከሳሹ) ሙግቱን ይከፍታል፡፡
  15. ሙግቱን የጀመረው ወገን ምስክሮቹ የሚመሰክሩለትን ነጥብ በአጭሩ ያስረዳል፡፡
  16. ምስክሮች እውነት ለመናገር ይምላሉ ወይም እውነት እንደሚናገሩ ያረጋግጣሉ፡፡
  17. ሙግቱን የጀመረው ሰው ምስክሮቹን አንድ በአንድ አቅርቦ ዋና ጥያቄ ይጠይቃል፡፡ ፍርድ ቤቱ በማንኛውም ሰዓት አስፈላጊ የሆነ ጥያቄ ይጠይቃል፡፡
  18.  ሙግቱን የከፈተው ወገን ምስክሮቹን አሰምቶ ከጨረሰ በኋላ ለሌላኛው ወገን ምስክሮቹን የሚያስረዱለትን የመከላከያ ነጥብ በአጭሩ አስረድቶ በተመሣሣይ ሁኔታ ምስክሮቹን ያሰማል፡፡
  19.  ማስረጃ የመስማቱ ሂደት ሲጠናቀቅ ግራ ቀኙ የመዝጊያ ቃላቸውን ይሰጣሉ
  20.  በመጨረሻም ፍርድ ቤቱ የፍርድ ውሳኔውን ይሠጣል

 ፍርድ
  1. የማስረጃ መሰማት ሥርዓት ተጣርቶ ካለቀ በኋላ ተከራካሪ ወገኖች የመዝጊያ (የማጠቃለያ) ቃላቸውን ይሰጣሉ፡፡ ሙግቱን የጀመረው ወገን መጀመሪያ ስለ ክርክሩ አጠቃላይ የመዝጊያ ቃሉን ይሰጣል፡፡ ከዚያ ሌላኛው ወገን ስለ ክርክሩ ያለውን አስተያየት በመዝጊያ ቃል ያቀርባል፡፡ በመጨረሻም ክርክሩን የጀመረው ወገን ለክርክሩ ያለውን ጠቅላላ የመዝጊያ ሐሳብ ያቀርባል
  2. የማስረጃ መሰማት ሥርዓቱ ተጣርቶ ካለቀና ከላይ የተጠቀሰው የመዝጊያ ቃል ከተሰጠ በኋላ ፍ/ቤቱ የፍርድ ውሳኔ ይሰጣል (ቁ.273)፡፡
  3. ለፍርድ ውሳኔው መሠረት ሊሆኑ የሚችሉ ማስረጃዎች፤

1. የምስክሮች ቃል (ባለጉዳዮቹ አቅራቢነት ወይም በፍ/ቤቱ ትዕዛዝ ቀርበው ቃላቸውን የሰጡ፣ በምትክ ዳኛ የተሰበሰቡ የምስክሮች ቃል ወይም ከፍ/ቤት ውጪ በመሃላ የተሰጡ የምስክሮች ቃል)፣

2. በኤክስፐርቶች የተሰጡ ማረጋገጫዎች፣

3. በባለጉዳዮቹ ወይም በፍ/ቤት ትዕዛዝ የቀረቡ የፅሑፍ ማስረጃዎችና ሰነዶች፣

4. በምትክ ዳኛ የተሰበሰቡ ሌሎች ማስረጃዎ፣

5. ባለጉዳዮች በፅሑፍ ወይም ፍርድ ቤቱ በሚመረምራቸው ጊዜ የሚሰጧቸው የእምነት ቃላት፣

6. ፍ/ቤቱ በቁ.272 መሠረት ባደረገው ምርመራ የተገኙ መረጃዎች፣

7.  የታወቁ ጉዳዮች (Judicial notice)፣

8.  በሕግ የተወሰደ የህሊና ግምት (Legal presumption)፣

9.  ያንድን ነገር አፈጣጠርና ሂደት ማሳያ (Demonstration)፣


10. ፍ/ቤቱ በዓይነት እንዲመለከታቸው የሚቀርቡለት ነገሮች (Exhibits) ሊያጠቃልል ይችላል፡፡

4. የእነዚህ ማስረጃዎች ተቀባይነት (Admissibility) እና እውነተኛነት (Credibility) ፍ/ቤቱ ይወስናል፡፡
5.  ባለጉዳዮቹ ወይም ወኪሎቻቸው የመክፈቻና የመዝጊያ ንግግር ሲያደርጉ ወይም ምስክሮችን በሚመረምሩበት ጊዜ የሚናገሯቸው ቃላት እንደማስረጃ መወሰድ የለባቸውም፡፡
6.  ከላይ በክፍል (ሠ) (3) ከተጠቀሰው ውጪ ዳው ከችሎት ውጭ ያያቸው ወይም የሰማቸው ነገሮች ወይም ያገኛቸው ማስረጃዎች ለውሳኔው መሠረት መሆን የለባቸውም፡፡
7. የቀረበው ክርክር ከተሰማ በኋላ ፍ/ቤቱ ነገሩ እንዳለቀ ወዲያውኑ ወይም በአጭር ቀነ ቀጠሮ በሚወስነው ጊዜ በግልጽ ችሎት ፍርድ መስጠት አለበት (ቁ.180)፡፡
8. የፍርድ አሰጣጥ፣ የውሳኔው አፃፃፍና ፎርም በቁ. 181 እና 183 በተደነገገው መሠረት መሆን አለበት፡፡
9.  በአንድ የፍርድ ሐተታ ላይ የተያዘው ጭብጥ፣ ጭብጡ እንዴት እንደተወሰነና የተወሰነበት ምክንያት መገለፅ አለበት፡፡ በመጀመሪያ ደረጃ የሚሰጥ ፍርድ ለክርክሩ መነሻ የሆነውን ዋነኛ ጉዳይ ባጭሩ የሚገልጽ መሆን አለበት (ቁ.182(1))፡፡
10. የመጀመሪያው ደረጃ ፍ/ቤት ተከራካሪዎቹ ወገኖች በዝርዝር ባላቀረቡት ወይም በግልጽ ባላመለከቱት ጉዳይ ላይ ፍርድ ለመስጠጥ አይችልም (ቁ.182(2))፡፡
11. በክርክሩ ላይ ከቀረቡት ብዙ ጭብጦች አንዱ ጭብጥ ብቻ ቢወሰን ሌሎቹንም ጭብጦች የሚያጠቃልል ከሆነ ክርክሩ ባንዱ ጭብጥ ብቻ ሊወሰን ይችላል፡፡ ካልሆነ ግን እያንዳንዱ ጭብጥ ለየብቻው ውሳኔ ማግኘት አለበት(ቁ.182(4))፡፡


Thursday, November 14, 2013

Civil Service Adminstrative Tribunal

This is the series on the DIFFERENT judicial tribunal in Ethiopia.
...........................
The civil service administrative tribunal is another judicial body that engage in adjudication of Civil Servant who are employed permanently by federal government institution. the scope of the law is limited to permanent civil servants and Government Institution that is to mean any federal government office established as an autonomous entity by a proclamation or regulations and fully or partially financed by government budget; included in the list of government institutions to be drawn up by the Council of Ministers. the Federal Civil Servants Proclamation Proclamation No. 515/2007 explain the structure and jurisdiction of the tribunal.

The tribunal is mandate to review Appeal or complaints of employees that are aggrieved by decisions of the head of a government institution. The administrative decisions are to be reviewed by administrative tribunal if  decision given by the Head of a government institution, either orally or in writing, on a recommendation by
disciplinary or grievance handling committee in accordance with the power conferred by law or a decision given by the Head of a government institution without following the required due process.

According to article 74 Administrative Tribunal have been Established. The major power of the Administrative Tribunal, includes to hear,litigates and decides cases brought to it. The Administrative Tribunal shall have chambers, which examine and decide on appeal cases. The proclamation further stressed that the tribunal is organized with different chamber that shall have a chairperson and two members designated by the General Director. The Administrative Tribunal shall have a power, given to an ordinary court under civil procedure code, to execute its own decision, decree , order and the court procedure . Regarding its independence the same article states that it is the Federal Civil Service Agency that decides on its activities. It particularly stressed that the Agency may issue directives relating to the way the judges perform their functions, the code of ethics they should observe, and other related matters.

According to article 75 the Jurisdiction of the Administrative Tribunal includes the power to hear and decide on appeals brought by a civil servant relating to:


1) unlawful suspension or termination of service;
2) being penalized by rigorous disciplinary penalty;
3)an illegal attachment or deduction of his salary or other payments;
4)infringement of his rights arising from an employment injury;
5) except provided in Article 73/7/ of this Proclamation ,cases investigated and decided upon by grievance handling committee
6)matters arising from his request for termination letters and testimonials of service.

The tribunal is barred to adjudicate cases relating to article 73(7).  Disciplinary measures provided under Article 73(7) refers to article 67/1//a/-/c/ which deals with the Types and Classification of Disciplinary Penalties. It particularly states that Depending on the gravity of the offence, one of the following penalties may be imposed on a civil servant for breach of discipline:
a) oral warning;
b) written warning;
c) fine up to one month’s salary;
The above power is given to the Grievance Handling Committee that is established according to article 72 of the proclamation.it particularly states that Any government institution shall establish a
grievance handling committee that conducts grievance inquiry, and submits recommendation to the Head of the government institution.. Furthermore according to article 73 Duties of Grievance Handling Committe includes investigation of complaints lodged by civil servants and submit recommendations especially relating to:-
1) interpretation and implementation of laws
and directives;
2) protection of rights and benefits;
3) occupational safety and health;
4) placement and promotion;
5) performance appraisal;
6) undue influence exerted by supervisors;
7) disciplinary measures provided under Article 67/1//a/-/c/;
8) other issues related to conditions of service.


The proclamation under article 76 states that the Administrative Tribunal may, after hearing the appeal, confirm or reverse the decision or vary the decision in favor of the appellant. Further the decision of the Administrative tribunal on question of facts shall be final; provided, however, that any one of the parties may appeal to the Federal Supreme Court on question of law within 30 days from the date of the decision of the Administrative Tribunal.

The proclamation under article 77 deals with the Execution of decision. it partiicularly affirms that Any government institution against which a decision is given by the Administrative Tribunal shall have the obligation to immediately execute the decision.Where the beneficiary of a decision pleaded that the decision of the Administrative Tribunal given in accordance with Article 76 of this Proclamation is not executed within 30 days, the Administrative Tribunal shall execute the decision.The Head of the government institution who failed to execute the decision of the Administrative Tribunal shall be liable for the damage sustained by the institution and the civil servant.
@legal advice and research in Ethiopia